ሁሉም ስፖንሰሮቻችን በኢትዮጵያ ውስጥ በሴቶች እና ህጻናት ህይወት ላይ ለውጥ ያመጣሉ። ጥቂቷም ሆነ ብዙው የእርሶ ወርሃዊ ስጦታ ትውልድ ይታደጋል፣ መልሶ ያቋቁማል እናም ህይወታቸውን ይለውጣል።

በተቋማችን ህገወጥ የሰው ዝውውርን እንዴት ማቆም እንደምንችል እናውቃለን። በመታደግ፣ በመልሶ ማቋቋም እና በሁለተናዊ ለውጥ ትግበራ በኢትዮጵያ ውስጥ የወሲብ ንግድን ማቆም እንችላለን። ጥረታችን ግን በወርሃዊ ስፖንሰሮቻችን ላይ የተመሰረተ ነው። ሁለት አይነት የስፖንሰርሺፕ ፕሮግራሞች አሉን። የመጀመሪያው የህፃናት ስፖንሰርሺፕ ፕሮግራም ሲሆን ይህም ዕድሜያቸው ከ8-15 የሆኑ ህጻናትን ህይወት መቀየር የምንችልበት ፕሮግራማችን ሲሆን፣ ሁለተኛው የሴቶች የስፖንሰርሺፕ ፕሮግራም ሲሆን ይህም ዕድሚያቸው ከ16-25 የሆናቸው ሴቶችን ህይወት ለማደስ እና ለመለወጥ የሚረዳ ፕሮግራም ነው።
የልጆች ስፖንሰርሺፕ ፕሮግራም:- ለአንድ ልጅ በየወሩ የሚለግሱት ገንዘብ ከታች የተዘረዘሩትን ጉዳዮችን ይሸፍናል:-
የአንድ ልጅ ስፖንሰር ይሆናሉ።
ኪራይ ይሸፍናል።
ምግብን ይሸፍናል።
መጓጓዣን ይሸፍናል።
Covers ከሽንት ቤት ጋር ተያያዥ ጉዳዮችን ይሸፍናል።
የሴቶች የስፖንሰርሺፕ ፕሮግራም:- ለአንዲት ሴት ልጅ በየወሩ የሚለግሱት ገንዘብ ከታች የተዘረዘሩትን ጉዳዮችን ይሸፍናል፡-
አንዲት ሴት ይታደጋል።
ኪራይ ይሸፍናል።
የሙያ ስልጠና ወጪዎችን ይሸፍናል።
ምግብን ይሸፍናል።
መጓጓዣን ይሸፍናል።
ከሽንት ቤት ጋር ተያያዥ ጉዳዮችን ይሸፍናል።

ማንኛውም ስፖንሰር በወሲብ ህገወጥ ዝውውር ለተጎዱት ደህንነትን እና ግብዓቶችን ለማቅረብ እኛን ለመርዳት ወሳኝ ሚና አለው። ስለ ለጋስነትዎ በጣም እናመሰግናለን።
ያግኙንSprings of Living Water | All rights reserved | Copyright © 2023